የወቅት መዝሙሮች
ተወዳጅ ልጅሽን ህማሙን ስታይ
ማሰብ ይሳነኛል የአንቺን ስቃይ
በእሾህ አክሊል ጉንጉን የቆሰለ ራሱንን
በብዙ ግርፋት/የታመመ አካሉ/(፪)
በዕፅ መስቀሉ የወረደ ደሙ
የቀራንዮ ግፍ እጅግ ማስገረሙ
ደጉ ልጅሽ ታስሮ የፍጥኝ ሲሰቃይ
ተሰክቶ ቀረ/ዓይንሽ ወደ ሰማይ/(፪)
ስለመሰቀሉ አይሁድ ሲደሰቱ
ሲስቁ ሲያሾፉ ቁማር ሲጫወቱ
ሲዘባበቱበት አይንሽ በማየቱ
ህሊናሽ ተገርፏል/በሀዘን በብርቱ/(፪)
ብላቴናይቱ የዳዊት ልጅ ማርያም
ስለደረሰብሽ ቢነገር አያልቅም
ተጠማው ቢላቸው መፃፃ አስጎነጩት
መርገም አስወግዶ/ቢሰጣቸው ሕይወት/(፪)
ለመጠጡ እንዲሆን መፃፃ ከሐሞት
ሰፍነግን ጨምረው በዘንግ አስጎነጩት
ዳዊት በትንቢቱ እንደተነበየው
በምግቤ መራራን/ጨመሩ እንዳለው/(፪)
ይኄ ሁሉ ሲሆን ድንግል ተመልክታ
መፅናናት ተሳናት በሐዘን ተነክታ
ኤሎሄ ኤሎሄ ጌታ ባለ ጊዜ
እጅግ ኃያል ነበር/የማርያም ትካዜ/(፪)
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምፅህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ
ከዋክብተ ሰማይበሙሉ ረገፉ
ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ
ሥጋህ በመስቀል ላይ ተጋልጦ ስላዩ
አዝ= = = = =
ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማርና ወተትን ለሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው
አዝ= = = = =
አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ
የገሊላ ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አሰብክ እንጂ ላንተስ አላሰብክ
አዝ= = = = =
እናቱ ስታለቅስ በመስቀል ሥር ሆና
ዮሐንስን ሰጣት ጠብቆ አንዲያጽናና
መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ
