በዘሩ የነበረች – – – ድንግል
የአዳም ተስፋ ዕንቁ ፀአዳ
የጽድቃችን ፀሐይ – – – ድንግል
የወጣባት ብርክት ሰሌዳ
ድንግል እናታችን ድንግል ሶልያና
በጸዳልሽ ታየን ከበርን እንደገና
ልጅሽ ልጅ አደረገን ዳግም እንደገና
ባዝኖ የነበረው – – – ድንግል
የተጎሳቆለ – – – ማርያም
በቀረችልን ዘር – – – ድንግል
አባቱን መሠለ – – – ማርያም
እንደ ሰዶም በሆንን ልክ እንደ ገሞራ
ውሃው ባይለወጥ ድንግል በአንቺ ስራ
አዝ= = = = =
የሴቲቱ ልጅ ነው – – – ድንግል
በአውሬው ራስ የቆመው – – – ማርያም
የጎደፈን ታሪክ – – – ድንግል
በደሙ ያረመው – – – ማርያም
እርሱን ስሙት ያለች አድርጉት በሙሉ
ፈቃዷ ፈቃዱ እግዚአብሔር ኃያሉ
አዝ= = = = =
ሰማይ ዙፋኑ ነው – – – ድንግል
ምድርም መረገጫው – – – ማርያም
የድንግል ማኅፀን – – – ድንግል
ሆነው መናገሻው – – – ማርያም
ስርጉተ ንጽሕና ጌታ አንቺን መረጠ
ጣዕም አልባነታችን በጨውሽ ጣፈጠ
አዝ= = = = =
ስለዚህ አርጋኖን – – – ድንግል
ስለዚህ በገና – – – ማርያም
ልቦና ያወጣው – – – ድንግል
ከፍሬ ሕሊና – – – ማርያም
የአንገታችን ማህተብ መዝገበ ልባችን
በጠበቀው ፍቅርሽ ለምኚ
